ለቦርድ እና የስታፍ አባላት የአንድ ቀን የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ By emwa In News 13 Oct 2023 አዲስ አበባ ጥቅምት 2፣ 2016 የፕላን ኢንተርናሽናል አማካሪ ተወካይ ለቦርድ እና ለ ስታፍ ሰራተኞች የስትራቴጂክ እቅድ አዘገጃጀት ላይ የአንድ ቀን የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጡ፡፡ስልጠናው ያስፈለገው ኢትመባሴማ ለሚያዘጋጀው የ አምስት አመት የስትራቴጂክ እቅድ ስለ እስትራቴጂክ እቅድ የግንዛቤ ደረጃን ለማሻሻል እና ስራውን በጥሩ ሁኔታ ለማከናወን እንደሚያግዝ በማሰብ ነው።በዚህም በስልጠናው የ ስትራቴጂክ እቅድ ምንነት ፣ አስፈላጊነት እና እንዴት መተግበር እንዳለበት ለሰልጣኞች ተብራርቷል፡፡